የኩፍኝ በሽታን ለማጥፋት ተባበሮ መስራት እንደሚያስፈልግ የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ

  • PDF

የአለም ጤና ድርጅት በኩፍኝ በሽታ  ምክንያት የሚሞቱትን የህፃናት ቁጥር ለመቀነስ ያስቀመጠው ግብ እንዳልተሳካ ገለጸ፡፡

በሽታውን በተመለከተ ላንሴት ለህትመት ያበቃው ትንታኔ እንደሚያሳየው እ.ኤ.አ ከ2000 እስከ 2010 ድረስ በኩፍኝ በሽታው የመሞት እድል 74 በመቶ % ብቻ በቀነሱ ተቀምጦ የነበረውን  90 ከመቶ ግብ  ማሳካት አልተቻለም ብሏል፡፡

አንዳንድ ተመራማሪዎች እንደሚገልጹት በሽታው በአፍሪካ መቀስቀሱና በህንድ የክትባት ፕሮግራሞቹ በመዘግየታቸው የተፈለገው መሻሻል እንዳልመጣ ነው፡፡

እ.ኤ.አ በ 2000 ዓ.ም  535, 300 ያህል ሰዎች የሞቱ ሲሆን   ይህ  ወደ 139,000 የወረደ ቢሆንም ከተቀመጠው አጠቃላይ ግብ አንጻር ሲታይ ግን የተፈለገውን ያህል መሄድ አልተቻለም፡፡

በዩኒሴፍ ዋና ዳይሬክተርና የኩፍኝና የትክትክ በሸታዎች ባለድርሻ አንቶኒዮ ሌክ እንደተናገሩት በአለም ላይ በኩፍኝ ምክንያት በየቀኑ 382 ያህል ሰዎች ይሞታሉ፡፡  “የሚሞቱት  በክትባቱ ህይወታቸውን ማትረፍ ይቻል ነበር” ብለዋል፡፡

እ.ኤ.አ በ 2015  በበሽታው የሚሞቱትን የሰዎች ቁጥር  በ95% ለመቀነስ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት ተባብሮ መስራት እነደሚያስፈልግም ተገልጿል፡፡

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት አስፈጻሚውን በመቆጣጠር ረገድ የጀመረውን ጠንካራ እርምጃ እንዴት ያዩታል?




Results

ለህዳሴ ግድብ ግንባታ የአባይን ወንዝ አቅጣጫ የማስቀልበስ ተግባር በኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ይከናወናል ብለው ገምተው ነበር




Results