20 June 2013
የኩፍኝ በሽታን ለማጥፋት ተባበሮ መስራት እንደሚያስፈልግ የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ
የአለም ጤና ድርጅት በኩፍኝ በሽታ ምክንያት የሚሞቱትን የህፃናት ቁጥር ለመቀነስ ያስቀመጠው ግብ እንዳልተሳካ ገለጸ፡፡
በሽታውን በተመለከተ ላንሴት ለህትመት ያበቃው ትንታኔ እንደሚያሳየው እ.ኤ.አ ከ2000 እስከ 2010 ድረስ በኩፍኝ በሽታው የመሞት እድል 74 በመቶ % ብቻ በቀነሱ ተቀምጦ የነበረውን 90 ከመቶ ግብ ማሳካት አልተቻለም ብሏል፡፡
አንዳንድ ተመራማሪዎች እንደሚገልጹት በሽታው በአፍሪካ መቀስቀሱና በህንድ የክትባት ፕሮግራሞቹ በመዘግየታቸው የተፈለገው መሻሻል እንዳልመጣ ነው፡፡
እ.ኤ.አ በ 2000 ዓ.ም 535, 300 ያህል ሰዎች የሞቱ ሲሆን ይህ ወደ 139,000 የወረደ ቢሆንም ከተቀመጠው አጠቃላይ ግብ አንጻር ሲታይ ግን የተፈለገውን ያህል መሄድ አልተቻለም፡፡
በዩኒሴፍ ዋና ዳይሬክተርና የኩፍኝና የትክትክ በሸታዎች ባለድርሻ አንቶኒዮ ሌክ እንደተናገሩት በአለም ላይ በኩፍኝ ምክንያት በየቀኑ 382 ያህል ሰዎች ይሞታሉ፡፡ “የሚሞቱት በክትባቱ ህይወታቸውን ማትረፍ ይቻል ነበር” ብለዋል፡፡
እ.ኤ.አ በ 2015 በበሽታው የሚሞቱትን የሰዎች ቁጥር በ95% ለመቀነስ የተያዘውን እቅድ ለማሳካት ተባብሮ መስራት እነደሚያስፈልግም ተገልጿል፡፡
| < Prev | Next > |
|---|


