|
አዲስ አበባ ሚያዝያ 29/2000 የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን
ኮርፖሬሽን በያዝነው በጀት ግማሽ ዓመት በሁሉም ዘርፎች የሚሰጠውን አገልግሎት የተሻለ
ውጤትና እድገት ማሳየቱን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
በ2000 በጀት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ውስጥ በሁሉም
የቴሌኮሙኒኬሽን ዘርፎች የተሻለ ጥረትና እንቅስቃሴ በመደረጉ የመደበኛ ቴሌፎን ደንበኞች
ወደ 920ሺ 63፣ የሞባይል ደንበኞች ወደ 1 ሚሊዮን 816 ሺ 946፣ የዲያል አፕ ወደ
28 ሺ 880 እንዲሁም የመልቲ ሚዲያ ደንበኞች ወደ 1ሺ 130 ከፍ ማለቱን ከኮርፖሬሽኑ
የተገኘ መረጃዎች ያመላክታሉ።
በመሆኑም ኮርፖሬሽኑ በያዝነው በጀት ግማሽ ዓመቱ መጨረሻ ላይ
በሰኔ 1999 በጀት ዓመት ከነበረው የመደበኛ ቴሌፎን ደንበኞች በ3.2 በመቶ፣ የሞባይል
ደንበኞች 50 በመቶ እና የመልቲ መዲያ ደንበኞች ደግሞ በ9.07 በመቶ እድገት ማሳየቱን
ያሳያል።
እንዲሁም በገጠር ቴሌኮም ውስጥ የተገናኙት የገጠር ቀበሌዎች ቁጥር
ከ7ሺ389 ወደ 9 ሺ 174 ከፍ በማለቱ የ24 በመቶ እድገት ማስመዝገቡን መረጃዎች
ያመላክታሉ።
በተመሳሳይ መልኩ በሰኔ 1999 ከነበረው የኔትዎርክ አቅምም
በመደበኛ ቴሌፎን 6.52 በመቶ፤ በሞባይል ቴሌፎን 65 በመቶ ከፍ ማለቱን ከኮርፖሬሽኑ
የተገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
የ2000 በጀት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የኮርፖሬሽኑ የአገልግሎት
ደረጃ ከ1999 በጀት መጨረሻ ጋር በንጽጽር የሚያሳይ ሰንጠረዥ ከዚህ በታች ቀርቧል።
|
የአገልግሎት/ኔትዎርክ አይነት
|
የኔትወርክ አቅም |
የደንበኛ ብዛት |
ለውጥ |
|
በኔትወርክ አቅም |
በደንበኞች |
|
ሰኔ 1999 |
ታህሳስ 2000 |
ሰኔ 1999 |
ታህሳስ 2000 |
በቁጥር |
% |
በቁጥር |
% |
|
የመደበኛ ቴሌፎን |
1,070,907 |
1,140,773 |
890,741 |
920,063 |
69,866 |
6.52 |
29322 |
3.2 |
|
የሞባይል ቴሌፎን |
1,375,000 |
2,278,516 |
1,208,498 |
1,816,946 |
903,516 |
65 |
608,448 |
50 |
|
የዲያልአኘ ኢንተርኔት |
100,000 |
100,000 |
31,400 |
28,880 |
- |
|
(2,600) |
(8.28) |
|
የመልቲሚዲያ ደንበኞች |
2.5G |
|
1,036 |
1,130 |
- |
|
94 |
9.07 |
|
ስኩልኔት |
|
|
625 |
636 |
|
|
11 |
1.76 |
|
የገጠር ቴሌኮም ደንበኞች |
|
|
7,389 |
9,174 |
|
|
1,785 |
24 |
ምንጭ፡-
የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን |