|
የፌዴራል መንግሥት ከ19 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ አደረገ |
||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||
|
አዲስ አበባ መጋቢት 16/2000 የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግሥት በያዝነው በጀት ግማሽ ዓመት ለመደበኛ፣ ለካፒታልና ለክልሎች የበጀት ድጋፍ ከ17 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ማድረጉን መረጃዎች ያመላክታሉ። ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የተገኙ መረጃዎች እንደሚያመላክቱት በበጀት ዓመቱ ለመደበኛ፣ ካፒታልና ለክልሎች የበጀት ድጋፍ ከታቀደው ብር 37 ቢሊዮን 784 ሚሊዮን ውስጥ 17 ቢሊዮን 352 ሚሊዮን 900 ሺህ ወይም የእቅዱን 46 በመቶ ያህሉን ማከናወኑን ያሳያሉ። በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት ለተለያዩ ተግባራት ማስፈፀሚያ ወጪ የተደረገው ገንዘብ መጠን ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ወጪ መጠን ጋር ሲነፃፀር የብር 1 ቢሊዮን 206 ሚሊዮን 700 ሺህ ወይም 31 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን መረጃዎች ጠቁሟል። ከአጠቃላይ ወጪ ውስጥ ለመደበኛ ወጪዎች የተከፈለው ብር 4 ቢሊዮን 88 ሚሊዮን 900 ሺህ የጠቅላላ ወጪውን 24 በመቶ የሚሸፍን ሲሆን፣ ለካፒታል ወጪዎች የተከፈለው ብር 6 ቢለዮን 766 ሚሊዮን ከጠቅላላው ወጪ 39 በመቶ ሲሆን በሌላ በኩል ለክልሎች የተላለፈ በጀት ድጋፍ ብር 6 ቢሊዮን 498 ሚሊዮን ሲሆን ይህም የጠቅላላ ወጪውን 37 በመቶ ድርሻ እንዳለው መረጃዎች ያመላክታሉ። የ2000 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ግማሽ የፌዴራል መንግሥት የመደበኛና የካፒታል ወጪ አፈፃፀም ከ1999 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አፈፃፀም ጋር በንፅፅር ሰንጠረዥ ከዚህ በታች ቀርቧል። በሚሊዮን ብር
ምንጭ፡- ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር |
||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||
|
|
|
|