የውጭ ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ቁጥር እድገት እሳየ

አዲስ አበባ የካቲት 12/2000 የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ በ2000 በጀት ዓመት የመጀመሪያ መንፈቅ ዓመት ውስጥ የኢንቨስትመንት ፈቃድ የሰጣቸው ፕሮጀክቶች በካፒታል መጠንና በሚፈጥሩት የሥራ እድል እድገት ማሳየቱን መረጃዎች ያመላክታሉ።

ከኤጀንሲው የተገኘ መረጃ እንደሚያመላክተው ከሐምሌ 1/1999 እስከ ታህሳስ 30/2000 ባሉት ጊዜያት ውስጥ በአጠቃላይ በሀገሪቱ በተለያዩ ክልሎች ከተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፍ ለሚሳተፍ 915 ፕሮጀክቶች ፈቃድ ተሰጥቷል።

ኤጀንሲው የኢንቨስትመንት ፈቃድ የተሰጣቸው 915 ፕሮጀክቶች በ30.283 ቢሊዮን ብር ካፒታል መጠን የሚንቀሳቀሱ ሲሆን ይህም ለ157,102 የሚሆኑ ዜጎች ቋሚ የሥራ እድል የፈጠሩ መሆኑን ጠቁሟል።

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ መንፈቅ ዓመት ውስጥ ኤጀንሲው የኢንቨስትመንት ፈቃድ ከሰጣቸው 915 ፕሮጀክቶች መካከል 847 የውጭ ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ሲሆኑ የውጭ ፕሮጀክቶች ድርሻ በቁጥር 92.6 በመቶ፣ በካፒታል መጠን ደግሞ 89.7 እንደሆነ መረጃው ያመላክታል።

እንዲሁም በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው መንፈቀ ዓመት ኤጀንሲው ፈቃድ የሰጣቸው የውጭ ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች በ1999 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ፈቃድ ከሰጣቸው የውጭ ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ጋር ሲነፃፀር በቁጥር 326 ፕሮጀክቶች ማለትም 62.6 በመቶ ከፍ ያለ መሆኑ ከኤጀንሲው የተገኘ መረጃ ያስረዳል።

በአጠቃላይ የኢንቨስትመንት ፈቃድ የተሰጣቸው ፕሮጀክቶች በካፒታል መጠንና በሚፈጥሩት ቋሚ የሥራ ዕድል ብዛት በየክፍለ ኢኮኖሚው እና የፕሮጀክቶቹ ክልላዊ ሥርጭት በሚቀጥሉት ሁለት ሰንጠረዦች ቀርቧል።

 ሠንጠረዥ 1፡- የኢንቨስትመንት ፈቃድ የተሰጣቸው ፕሮጀክቶች ክፍለ ኢኮኖሚ ያዊ ስርጭት ፣ የካፒታል መጠንና የሚፈጥሩት ቋሚ የሥራ ዕድል ብዛት ግምት (ሐምሌ 1/1999 - ታህሣሥ 30/2000)

 

 

 

ተ.ቁ

 

 

ክፍለ ኢኮኖሚ

 

የፕሮጀክት

 

የኢንቨስትመንት ካፒታል መጠን

የሚፈጠር ቋሚ የሥራ ዕድል ግምት

 

ብዛት

 

%

 

ቢሊዮን ብር

 

%

 

ብዛት

 

%

1

ግብርና

158

17.27

4.895

16.16

119219

75.89

2

የኮንስትራክሽን ሥራ ተቋ.

27

2.95

0.321

1.06

1085

0.69

3

ትምሕርት

40

4.37

0.435

1.44

1697

1.08

4

የጤናና የማሕበራዊ ሥራ

35

3.83

0.890

2.94

2900

1.85

5

የኤሌክትሪክ ፣ ጋዝ ፣ የእንፋሎትና የውሃ አቅርቦት

4

0.44

2.487

8.21

168

0.11

6

የሆቴልና ቱሪዝም

93

10.16

4.125

13.62

2851

1.81

7

የማምረቻ ኢንዱስትሪ

244

26.67

11.674

38.55

23379

14.88

8

የሕንፃ ግንባታ

34

3.72

3.973

13.12

2370

1.51

9

የኮንስትራክሽንና ሌሎቸ መሣሪያዎች ኪራይ አገልገሎት

225

24.59

1.139

3.76

2547

1.62

10

የትራንስፖርት ፣ የመጋዘንና የመገናኛ አገልግሎት

40

4.37

0.119

0.39

614

0.39

11

የጅምላ ንግድ ፣ የችርቻሮ ንግድና የጥገና አገልግሎት

9

0.98

0.189

0.62

172

0.11

12

ሌሎች [1]

6

0.66

0.036

0.12

100

0.06

 

ድምር

915

100

30.283

100

157102

100

 

 

 

ሠንጠረዥ 2፡-የኢንቨስትመንት ፈቃድ የተሰጣቸው ፕሮጀክቶች ክልላዊ ስርጭት በካፒታል መጠን (ሐምሌ 1/1999 - ታህሣሥ 30/2000)

 

 

 

ተ.ቁ

 

 

ክልል/አስተዳደር

 

የኢንቨስትመንት ካፒታል መጠን

 

ቢሊዮን ብር

 

%

1

አዲስ አበባ

7.94

26.2

2

አፋር

0.10

0.33

3

አማራ

2.44

8.06

4

ቤንሻንጉልና ጉምዝ

0.03

0.09

5

ድሬዳዋ

2.24

7.41

6

ጋምቤላ

0.003

0.01

7

ኦሮሚያ

10.51

34.71

8

ደቡብ ብ/ብ/ሕ

1.44

4.76

9

ትግራይ

0.22

0.74

10

በተለያዩ ክልሎች[2]

5.36

17.68

 

ድምር

30.283

100

 


 

ምንጭ፡- የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ