|
የሀገር ውስጥ ገቢ መ/ቤት ከ4 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰበሰበ |
||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||
|
አዲስ አበባ ጥር 28/2000 የኢትዮጵያ ሀገር ውስጥ ገቢ ባለሥልጣን በያዝነው በጀት ዓመት ስድስት ወራት ውስጥ ከግብር እና ከታክስ ከ4 ቢሊዮን 298 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን መረጃዎች ያመላክታሉ። ከሀገር ውስጥ ገቢ ባለሥልጣን መ/ቤት የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው ከሐምሌ 1/1999 እስከ ታህሳስ 30/2000 ድረስ ባሉት ጊዜያት ከቀጥታ ታክሶችና ቀጥታ ያልሆኑ ታክሶች እንዲሁም ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች ብር 4 ቢሊዮን 20 ሚሊዮን 50 ሺህ ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ ብር 4 ቢሊዮን 298 ሚሊዮን 53 ሺህ ማለትም የእቅዱን 106.92 በመቶ መሰብሰቡን ያሳያል። በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት ውስጥ የተሰበሰበው ገቢ ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በብር 1 ቢሊዮን 179 ሚሊዮን 45 ሺህ ወይም የ137.81 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑን መረጃው ይጠቁማል። ለገቢ አሰባሰቡ አወንታዊ አስተዋፅኦ እንዲኖራቸው ካደረጉ ምክንያቶች ውስጥ መረጃዎችን ሰብስቦና አጠናቅሮ ለታክስ ገቢ ሰብሳቢ ማዕከላት በመሰራጨቱ፣ የደረሱ የህትመት ፈቃድ በመሰጠቱ፣ ግብይት በደረሰኝ ለመከናወኑ ክትትል በመደረጉ እና የታክስ ኦዲት ሥራዎች በግማሽ ዓመቱ በአግባቡ በመከናወናቸው መሆኑን መረጃው ያመላክታል። የ2000 በጀት ግማሽ ዓመት የገቢ እቅድ ክንውንና የ1999 በጀት ግማሽ ዓመት የገቢ ክንውን ቀጥሎ ባለው ሰንጠረዥ ቀርቧል። b¸lþ×N BR
ምንጭ:- የሀገር ውስጥ ገቢ ባለሥልጣን |
||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||||
|
|
|
|