የንግድ መርከብ አክሲዮን ማህበር ከ1 ሚሊዮን ቶን በላይ እቃዎች አጓጓዘ

አዲስ አበባ ሚያዚያ 15/2000 የኢትዮጵያ ንግድ መርከብ አክሲዮን ማህበር በ2000 ግማሽ ዓመት በወጪና ገቢ እቃዎች ከ1 ሚሊዮን ቶን በላይ እቃዎች መጓጓዙን መረጃው ጠቋሟል።

ከኩባንያው የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በበጀት ግማሽ ዓመቱ ውስጥ በወጪ እቃ፣ በገቢ እቃ እንዲሁም በውጭ ሀገር ወደቦች መካከል የተጓጓዘውን ጨምሮ 860 ሺ 677 ቶን ዕቃ ለማጓጓዝ አቅዶ 1 ሚሊዮን 203 ሺህ 139 ቶን ማለትም የእቅዱ 140 በመቶ ማከናወኑን ያሳያል።

ኩባንያው በበጀት ግማሽ ዓመቱ ውስጥ ለማጓጓዝ የቻለው እቃ ካለፈው ዓመት ተመሣሣይ ወቅት ክንውን ጋር ሲነፃፀር የ66 በመቶ ብልጫ እንዳለው ያሳያል።

ክንውኑ ሊበልጥ የቻለው የሃገሪቷን የውጭ ንግድ ከመጨመሩ ጋር በተያያዘ ኩባንያው በራሱ መርከቦች እንዲሁም በተጠናከረ መልኩ የኪራይ የመርከብ ድርጅቶችን መርከቦች የጭነት ቦታ ተከራይቶ በመስራቱ መሆኑን መረጃው ያስረዳል።

በግማሽ ዓመቱ ውስጥ ከተጓጓዘው እቃ 393 ሺ 267 ቶን ወይም 33 በመቶ በኩባንያው መርከቦች ሲሆን 809 ሺ 872 ቶን ወይም 67 በመቶ ደግሞ በኪራይ መርከቦች መሆኑን ጠቋሟል።

በግማሽ ዓመቱ ውስጥ ከተጓጓዘው እቃ መጠን ውስጥ 48 በመቶ ያህሉ በኮንቴይነር ታሽጐ  የተጓጓዘ ሲሆን 7 በመቶ በመኪና ጭነት እንዲሁም 45 በመቶ ጥቅል ዕቃዎች ጭነት መሆኑን ከኩባንያው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።   

¾ኩባንያው የ2000 ግማሽ  ¯Sƒ  ¾›ÑMÓKAƒ °pÉ ›ðíìU በሚቀጥለው ሰንጠረዥ ቀርቧል

                                                                                                                                                    u„”

ተ.ቁ

 

የ1999 ክንውን

የ2000 ዕቅድ

የ2000 ክንውን

የ2000 ክንውን

ከዕቅድ (%)

ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ልዩነት

1

የግማሽ ዓመቱ

 

 

 

 

 

 

1.1. ዓለም አቀፍ አገልግሎት

 

 

 

 

 

 

     ገቢ ዕቃ

716,627

845,177

1,069,808

127

49

 

        በኩባንያው መርከቦች

155,632

216,215

260,944

121

68

 

        በኪራይ መርከቦች

560,995

628,962

808,864

129

44

 

    ወጪ ዕቃ

3222

5,500

2659

48

-17

 

      በኩባንያው መርከቦች

2937

5,500

2,609

47

-11

 

      በኪራይ መርከቦች

285

0

50

 

-82

 

   ገቢና ወጪ ዕቃ

719,849

850,677

1,072,467

126

49

 

      በኩባንያው መርከቦች

158,569

221,715

263,553

119

66

 

      በኪራይ መርከቦች

561,280

628,962

808,914

129

44

 

1.2. በውጪ ሀገር ወደቦች መካከል

3,531

10,000

130,672

1307

3601

 

      በኩባንያው መርከቦች

3,531

10,000

129,714

1297

3574

 

      በኪራይ መርከቦች

0

0

958

 

 

 

1.3.